አምዶች

Logo ከይር ታይምስ

የዲጂታል ዜና እምብርት

የቅርብ
“የፉክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል”፤ መምህር ታዬ ቦጋለ የፖሊሲ ነፃነት ሚስጥር፤ ኢትዮጵያ ቁልፍ መረጃዎቿን በራሷ እጅ ማድረጓ ምን ትርጉም አለው? 'ምንም የሚተርፍ ነገር አይኖርም’ የትራምፕ ለኢራን የሰጡት ማስጠንቀቂያ ህወሓትን ከሥልጣን ለማስወገድ ያለመው አዲሱ ምክር ቤት እና የጀነራሎቹ ወታደራዊ ስልት የሕዝብ እንደራሴዎች ወይስ የፖለቲካ ምስጢረኞች? ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ የዕዳ መልሶ ማዋቀሪያ ሥርዓት በአስቸኳይ እንዲሻሻል ጠየቀች መንግስት ከሕዝብ እይታ የሸሸገውን የፋይናንስ ምንጭ በግልጽ ለሕዝብ ይፋ ሊያደርግ ይገባል FIFTY MAJOR POLITICAL THINKERS የማክሮን የአፍሪካ ጉዞ እና የኃያልነት ስጋት ቻይና ከአሜሪካ ነዳጅ ለመግዛት ተስማማች፤ ትራምፕ የቤጂንግ ጉብኝታቸውን አጠናቀቁ “የፉክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል”፤ መምህር ታዬ ቦጋለ የፖሊሲ ነፃነት ሚስጥር፤ ኢትዮጵያ ቁልፍ መረጃዎቿን በራሷ እጅ ማድረጓ ምን ትርጉም አለው? 'ምንም የሚተርፍ ነገር አይኖርም’ የትራምፕ ለኢራን የሰጡት ማስጠንቀቂያ ህወሓትን ከሥልጣን ለማስወገድ ያለመው አዲሱ ምክር ቤት እና የጀነራሎቹ ወታደራዊ ስልት የሕዝብ እንደራሴዎች ወይስ የፖለቲካ ምስጢረኞች? ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ የዕዳ መልሶ ማዋቀሪያ ሥርዓት በአስቸኳይ እንዲሻሻል ጠየቀች መንግስት ከሕዝብ እይታ የሸሸገውን የፋይናንስ ምንጭ በግልጽ ለሕዝብ ይፋ ሊያደርግ ይገባል FIFTY MAJOR POLITICAL THINKERS የማክሮን የአፍሪካ ጉዞ እና የኃያልነት ስጋት ቻይና ከአሜሪካ ነዳጅ ለመግዛት ተስማማች፤ ትራምፕ የቤጂንግ ጉብኝታቸውን አጠናቀቁ
ዜና ትንታኔ

“የፉክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል”፤ መምህር ታዬ ቦጋለ

የታዋቂው የታሪክ ምሁርና የፖለቲካ ተንታኝ መምህር ታዬ ቦጋለ አረጋ በይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት እጅግ ጠንካራና ወቅታዊ መልዕክት፣ በአንዳርጋቸው ፅጌ የቅርብ ጊዜ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችና “የእንጨት ሽበት ነውረኝነት” ላይ ያነጣጠረ ስለታም ትንታኔ ሰንዝረዋል። መምህር ታዬ በጽሑፋቸው፣ ዕድሜ ሁልጊዜም ለሀገርና ለወገን ማሰብን እንደማያወርስ በመጥቀስ፣ የያዘውን የታሪክ ስብራትና ጥላቻ ይዞ ወደ መቃብር አፋፍ እየተጓዘ ያለው ያ ዘመን ትውልድ ዛሬም ሀገርን ወደ ለየለት እልቂት ለመምራት ክብሪት እየጫረ መሆኑን በጥብቅ አስጠንቅቀዋል። አንዳርጋቸው ፅጌ ከ50 ዓመታት በፊት በ24 ዓመት ወጣትነቱ ኢትዮጵያን ጥሎ በሱዳን በኩል መሰደዱን ያስታወሱት ታዬ ቦጋለ፣ ከአምስት አስርት ዓመታት በኋላ በድጋሚ በፖርት ሱዳን መድረክ ላይ ተገኝቶ ያደረገው ንግግር ግን እጅግ መርዘኛና አደገኛ መሆኑን አጋልጠዋል። አንዳርጋቸው ሱዳንን “ባለውለታ” ካለ በኋላ፣ “የኢትዮጵያ መንግሥት ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች (UAE) በመወገን ሱዳንን ለማፍረስ እየሠራ ነው” በማለት በሱዳንና በኢትዮጵያ መካከል ጦርነት ለመለኮስ ያለመ ንግግር ማድረጉን ጠቅሰዋል። መምህር ታዬ “የእንግሊዝ (UK) ዜጋ የሆነውና ከሃምሳ ዓመታት በላይ ውጪ ሀገር የኖረው ይህ ግለሰብ በዚህ የጃጀ ዕድሜው ፖርት ሱዳን የተገኘው ማንን ወክሎ ነው?” ሲሉ ጠንካራ ጥያቄ ሰንዝረዋል። መምህር ታዬ ቦጋለ አንዳርጋቸው ፅጌ “እኛም እንናገር፤ ትውልድ አይደናገር” በተሰኘው መጽሐፉ ያነገበውን ፍጹም ነውረኛ ጥላቻ ይፋ አድርገዋል። ግለሰቡ “አማራ የሚባል ብሔር የለም” ከማለቱም በላይ፣ የአማርኛ ቋንቋን “ወታደሮች ለምሥጢራዊ መግባቢያነት የፈጠሩት የወፍ ቋንቋ ነው” ሲል የገለጸበትን አግባብ በጥብቅ አውግዘዋል። በተጨማሪም “ከዐድዋ ጦርነት በኋላ ዳግማዊ ምኒልክ የተሰዋውን ክርስቲያን ፍትሐት አስደርገው በክብር ሲያስቀብሩ፣ ሙስሊም ሰማዕታትን ግን ሥጋቸውን አሞራ እና ጅብ እንዲበላው በየሜዳው ጥለውት ሄዱ” በማለት አንዳርጋቸው ያስደጎሰው ጦማር፣ በኢትዮጵያውያን መካከል የማያባራ የሃይማኖትና የብሔር ቁርሾ ለመትከል የታለመ ስልታዊ የጥፋት ፖለቲካ መሆኑን የታሪክ ምሁሩ አረጋግጠዋል። ታዬ ቦጋለ አንዳርጋቸው ፅጌ በትግራይ ወገናችን ላይ የዘር ማጥፋት (Genocide) ቅስቀሳ ሲያደርግ እንደነበርና ነገ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሕግ እንደሚጠየቅ ጠቅሰው፣ አሁን ደግሞ ይባስ ብሎ ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ሊያፈርሱ የሚችሉ ኃይሎችን በአንድ ላይ የመጣመር አደገኛ ጥሪ እያቀረበ መሆኑን አጋልጠዋል፦ • ከአማራ ክልል መሬት የምትሻውን ሱዳንን፣ • ከትግራይ ሰፊ መሬት የሚፈልገውን ሻዕቢያን፣ • የወሰን ውዝግብ ያላቸውን ሕወሓትንና በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰውን ኃይል በጽምዶ አጣምሮ ኢትዮጵያን የማፍረስ የተረገመ ጥሪ እያስተጋባ ይገኛል። ታዬ ቦጋለ በጥያቄያቸው፡ “ይህ አረመኔ ግለሰብ ማንን ወክሎ ነው ይህንን ምስቅልቅል የሚፈጥረው? የለም ብሎ የካደውን አማራን? ሕወሓትን? ሻዕቢያን? ወይስ ሱዳንን?” ካሉ በኋላ፣ ምላሹን ለኢትዮጵያ ሕዝብ በመተው የውስጥ ባንዳዎችና የውጭ ባዳዎች በሕብረት በመጣመድ ሀገራችንን ወደለየለት እልቂት ለመምራት የተቀናጀ እቅድ ይዘው መነሳታቸውን አስገንዝበዋል። የታሪክ ምሁሩ መልዕክታቸውን ሲያጠቃልሉ ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የሞት ሽረት ጥሪ አቅርበዋል። “ለውስጥ ፀቡ፣ ብሽሽቁና ልፊያው በኋላ እንደርስበታለን፤ ከሁሉም ሀገር ይቀድማል” ያሉት መምህር ታዬ፣ የፉክክር ቤት ሳይዘጋ እንደሚያድር በማስታወስ፣ በአንድ ወቅት በቸልተኝነትና በስሜት የተረተረነውን ሀገር መልሰን በስሌት ለመስፋት ብንሞክር ዋጋው የከበደ እንደሚሆንና ሁላችንም የፀፀትን ዋጋ እንደምንከፍል አስገንዝበዋል። ወጣቱ ትውልድ አፍ ከልብ ሆኖ ሀገሩን ለማዳን መሰለፍ እንዳለበት በመጠቆም፣ ከተንኮለኞች ሴራ ራሱን አርቆ ለመከላከያ ሠራዊታችን፣ ለብሔራዊ መረጃና ደኅንነት፣ ለፌደራል ፖሊስና ለመላው መለዮ ለባሾች እውቅናና ክብር በመስጠት ከሰላም ዘብ ጎን እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።

አርዕስተ ዜና — May 19, 2026
Advertisement
Milkii Advertisement

አበይት ዜናዎች

አስተያየት

በቋፍ ያለው የኢትዮጵያና የአፍሪካ ቀንድ ጂኦ-ፖለቲካ

የአፍሪካ ቀንድ በአሁኑ ወቅት በታሪኩ አይቶት የማያውቀው እጅግ ውስብስብና አሳሳቢ የፖለቲካና የፀጥታ ቀውስ ውስጥ ይገኛል። በኢትዮጵያ የውስጥ ፖለቲካ ውስጥ እየታዩ ያሉ አዳዲስ ክስተቶች እና በጎረቤት ሀገራት መካከል የሚስተዋሉ የዲፕሎማሲ...

ዓለም አቀፍ ዜና

'ምንም የሚተርፍ ነገር አይኖርም’ የትራምፕ ለኢራን የሰጡት ማስጠንቀቂያ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ጦርነት ዙሪያ ወደፊት ስለሚወሰዱ እርምጃዎች ለመወያየት ቅዳሜ ዕለት ከብሔራዊ ደኅንነት ቡድናቸው ከፍተኛ አባላት ጋር መገናኘታቸውን ሲ.ኤን.ኤን ዘግቧል። ይህ ስብሰባ የተደረገው ቴህራን “በፍጥነ...

ዲፕሎማሲ

ኢትዮጵያና አሜሪካ ስትራቴጂካዊ ግንኙነታቸውን ይበልጥ የሚያጠናክር ስምምነት ተፈራረሙ

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ለዘመናት የዘለቀውን ታሪካዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግር የሁለትዮሽ መዋቅራዊ ውይይት ማዕቀፍ ስምምነት በዋሽንግተን ዲሲ ተፈራረሙ...

ዓለም አቀፍ ዜና

ቻይና ከአሜሪካ ነዳጅ ለመግዛት ተስማማች፤ ትራምፕ የቤጂንግ ጉብኝታቸውን አጠናቀቁ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቻይና ከአሜሪካ ከፍተኛ መጠን ያለው ነዳጅ ለመግዛት እና ከዋሽንግተን ጋር ያላትን የንግድ አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር መስማማቷን አስታውቀዋል። ፕሬዚዳንቱ ይህንን ይፋ ያደረጉት በቤጂንግ የነበራቸውን...

እኔ እምለው

መንግስት ከሕዝብ እይታ የሸሸገውን የፋይናንስ ምንጭ በግልጽ ለሕዝብ ይፋ ሊያደርግ ይገባል

ከሰሞኑ በዓድዋ መታሰቢያ ሙዚየም በተካሄደው “አዲሲቷ አዲስ አበባ” የውይይት መድረክ ላይ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ የተናገሩት ንግግር የከተማዋን ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን ማ...

ዓለም አቀፍ ዜና

የማክሮን የአፍሪካ ጉዞ እና የኃያልነት ስጋት

ኤማኑኤል ማክሮን ከማንኛውም የቀድሞ የኤልዛቤ (ፈረንሳይ) ፕሬዝዳንት በላይ የአፍሪካን ምድር ረግጠዋል። ለደጋፊዎቻቸው ይህ ተደጋጋሚ ጉዞ ዘመናዊ እና ንቁ የውጭ ፖሊሲ ማሳያ ነው። ለተቺዎቻቸው ግን ከአህጉሪቱ ተፅዕኖዋ እየመነመነባት ያለች...

የሀገር ውስጥ ዜና

የትግራይ ፕሬዝዳንት በሳውዲ አረቢያ ለሞት የተፈረደባቸው ዜጎች ምህረት እንዲደረግላቸው ተማጸኑ

የትግራይ ፕሬዝዳንት ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በሳውዲ አረቢያ መንግስት የሞት ፍርድ ለተበየነባቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች ምህረት እንዲደረግላቸው የሚጠይቅ ይፋዊ የልመና ደብዳቤ አቀረቡ። ፕሬዝዳንቱ ለሳውዲ አረቢያ የ...

የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉ የዕዳ መልሶ ማዋቀሪያ ሥርዓት በአስቸኳይ እንዲሻሻል ጠየቀች

በማደግ ላይ ያሉ አገራትን ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሁኔታ ከግምት ውስጥ ያላስገቡ የዓለም አቀፍ የፋይናንስ እና የንግድ ሥርዓቶች በአስቸኳይ መዋቅራዊ ማሻሻያ ሊደረግባቸው እንደሚገባ ኢትዮጵያ ጥሪ አቀረበች። ሀገሪቱ ይህንን ጥሪ ያደረገችው በሕን...

የፖለቲካ ፓርቲዎች

ህወሓትን ከሥልጣን ለማስወገድ ያለመው አዲሱ ምክር ቤት እና የጀነራሎቹ ወታደራዊ ስልት

በሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ላይ ጠንካራ የተቃውሞ አቋም የያዙ የፖለቲካ እና የጦር መሪዎች፣ በትግራይ ክልል ላይ የፖለቲካና የወታደራዊ የበላይነትን መልሶ ለመያዝ ያለመ “የትግራይ ሰላምና ለውጥ ምክር ቤት&rdquo...

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ