አምዶች

Logo ከይር ታይምስ

የዲጂታል ዜና እምብርት

የቅርብ
አርቲፊሻል ለውጥ ወይስ እውነተኛ የአካዳሚክ ነፃነት? የጽምዶ እና የመከላከያ ውጥረት እስከም ድረስ ይሆን? ጎጎት ፓርቲ የገዢው ፓርቲ "ስልታዊ" የምርጫ ሕግ ጥሠቶች" ካልታረሙ ራሱን ከምርጫው እንደሚያገል አስጠነቀቀ ኬንያ ከኢትዮጵያ የምታስገባውን የኤሌክትሪክ ኃይል በእጥፍ ልታሳድግ መኾኑ ተገለጠ 📢 አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክት ከገንዘብ ሚኒስቴር! ⚠️ ምርጫ ቦርድ የዕጩ ይስሃቅ ወልዳይን ራስን ከምርጫ የማግለል ውሳኔ ውድቅ አደረገ “የኮከቡ ሰው” የተሰኘው አዲስ ተውኔት ነገ በዓለም ሲኒማ ለተመልካች ሊቀርብ ነው የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ለታዳጊ አገራት አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠየቁ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚፈጸሙ ከሕግ አግባብ ውጪ የሆኑ እስራቶችና የመብት ጥሰቶች አሁንም አሳሳቢ መሆናቸውን ኢሰመኮ ገለጸ ፌደራል ፖሊስ በእነ ጀነራል አስናቀው ሲሳይ ላይ ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጠየቀ አርቲፊሻል ለውጥ ወይስ እውነተኛ የአካዳሚክ ነፃነት? የጽምዶ እና የመከላከያ ውጥረት እስከም ድረስ ይሆን? ጎጎት ፓርቲ የገዢው ፓርቲ "ስልታዊ" የምርጫ ሕግ ጥሠቶች" ካልታረሙ ራሱን ከምርጫው እንደሚያገል አስጠነቀቀ ኬንያ ከኢትዮጵያ የምታስገባውን የኤሌክትሪክ ኃይል በእጥፍ ልታሳድግ መኾኑ ተገለጠ 📢 አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክት ከገንዘብ ሚኒስቴር! ⚠️ ምርጫ ቦርድ የዕጩ ይስሃቅ ወልዳይን ራስን ከምርጫ የማግለል ውሳኔ ውድቅ አደረገ “የኮከቡ ሰው” የተሰኘው አዲስ ተውኔት ነገ በዓለም ሲኒማ ለተመልካች ሊቀርብ ነው የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ለታዳጊ አገራት አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠየቁ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚፈጸሙ ከሕግ አግባብ ውጪ የሆኑ እስራቶችና የመብት ጥሰቶች አሁንም አሳሳቢ መሆናቸውን ኢሰመኮ ገለጸ ፌደራል ፖሊስ በእነ ጀነራል አስናቀው ሲሳይ ላይ ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጠየቀ
የምሁራን መድረክ

አርቲፊሻል ለውጥ ወይስ እውነተኛ የአካዳሚክ ነፃነት?

ሰሞኑን በትምህርት ሚኒስቴር ይፋ የተደረገው አቅጣጫ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አመራሮች አመዳደብ ቀድሞ ከነበረው የብሔር ስብጥር አሰራር በመውጣት በችሎታ በቻ ተወዳድረረው የሚመደቡበት አሠራር ሊዘረጋ እንደሆነ ያሳያል። ይህ ውሳኔ በአንደኛ እይታ እንደ ትልቅ “ሪፎርም” እና ተስፋ ሰጪ እርምጃ ሊታይ ይችላል። ይሁን እንጂ፣ የሀገሪቱን ነባራዊ የፖለቲካ ልምድ እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የተወሳሰበ ውድቀት መነሻ በማድረግ፣ ጉዳዩን ይበልጥ በጥልቀት ስንመረምረው፣ ከጀርባው ያሉትን ስር የሰደዱ ጥያቄዎች እና ስጋቶች መገንዘብ ያስፈልጋል። የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላለፉት በርካታ አስርት ዓመታት የብሔር ፖለቲካ መፈልፈያ፣ የፓርቲ ካድሬዎች መደበቂያ እና የብቃት ማነስ ማሳያ ሆነው መቆየታቸው የአደባባይ ምስጢር ነው። አሁን ላይ “ከብሔር ስብጥር አሰራር ወጥተን በችሎታ ልንመድብ ነው” ተብሎ የሚነገረው ትረካ፣ ተቋማቱ አስከፊ የጥራት መውረድ አጋጥሟቸው፣ የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት ተማሪዎች ሳይሆኑ ተቋማቱ ራሳቸው የወደቁ መሆናቸውን ካረጋገጠ በኋላ የመጣ የኋሊት ጩኸት ነው። ይህ መዘግየት በራሱ የፖለቲካው ውሳኔ የትምህርትን መዋቅር ምን ያህል እንዳደቀቀው ማሳያ ነው። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዩኒቨርሲቲዎችን “ከማንኛውም የፖለቲካ ተፅዕኖ ነፃ ማድረግ” ስለሚለው አጀንዳ ደጋግመው ይናገራሉ። ይሁን እንጂ፣ በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ “ክፍት ውድድር” የሚባሉ የቅጥር ማስታወቂያዎች ራሳቸው በፖለቲካ ታማኝነት (Political Loyalty) እና በውስጥ መስመር ውሳኔዎች የሚጠለፉባቸው አጋጣሚዎች በርካታ ናቸው። ተቋማቱ በተግባር ነፃነታቸው ሳይረጋገጥ፣ በወረቀት ላይ በሚደረግ “ፈተና እና ውድድር” ብቻ አመራር ለመቀየር መሞከር፣ የድሮዎቹን ካድሬዎች በአዲሱ ገዥ መደብ ፍላጎት በሚስማሙ አዳዲስ “ቴክኖክራቶች” ከመተካት የዘለለ መዋቅራዊ ለውጥ ላያመጣ ይችላል። እውነተኛ ነፃነት የሚለካው አመራሩ በሚመረጥበት መንገድ ብቻ ሳይሆን፣ ተቋማቱ ከመንግስት ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው በራሳቸው መተዳደር (Autonomy) ሲችሉ ብቻ ነው። ዩኒቨርሲቲዎች በአሁኑ ወቅት የተጋረጡባቸው ችግሮች የአመራሮቹ የብሔር ስብጥር ብቻ አይደለም። ተቋማቱ በከፍተኛ የበጀት እጥረት፣ በደህንነት ስጋቶች፣ በካምፓስ ውስጥ አለመረጋጋት፣ እና በተመራማሪዎች የኑሮ መጓደል ሳቢያ ምሁራንን እያጡ ያሉ አቅመ-ቢስ መዋቅሮች ሆነዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ (ለምሳሌ በዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ ቀውሶች ሳቢያ በሚከሰት የኢኮኖሚ ጫና) የሚታየው የዋጋ ንረት እና የሪሶርስ እጥረት ባለበት ሁኔታ፣ የአመራር መምረጫ መስፈርቱን “በእውቀትና ችሎታ” ላይ ብቻ አደረግን ማለት ብቻውን ተቋማቱን የጥናትና ምርምር ማዕከል ሊያደርጋቸው አይችልም። መዋቅራዊ እና ፋይናንሺያል ድጋፍ ሳይኖር፣ ብቁ መሪዎችን ብቻ ወደ ወንበር ማምጣት በባዶ ሞተር ላይ ጎበዝ ሾፌር የማስቀመጥ ያህል ነው።  

አርዕስተ ዜና — May 24, 2026
Advertisement
Milkii Advertisement

አበይት ዜናዎች

ዓለም አቀፍ ዜና

'ምንም የሚተርፍ ነገር አይኖርም’ የትራምፕ ለኢራን የሰጡት ማስጠንቀቂያ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ጦርነት ዙሪያ ወደፊት ስለሚወሰዱ እርምጃዎች ለመወያየት ቅዳሜ ዕለት ከብሔራዊ ደኅንነት ቡድናቸው ከፍተኛ አባላት ጋር መገናኘታቸውን ሲ.ኤን.ኤን ዘግቧል። ይህ ስብሰባ የተደረገው ቴህራን “በፍጥነ...

ዜና ትንታኔ

“የፉክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል”፤ መምህር ታዬ ቦጋለ

የታዋቂው የታሪክ ምሁርና የፖለቲካ ተንታኝ መምህር ታዬ ቦጋለ አረጋ በይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት እጅግ ጠንካራና ወቅታዊ መልዕክት፣ በአንዳርጋቸው ፅጌ የቅርብ ጊዜ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችና “የእንጨት ሽበት ነው...

እውነት ወይስ ሀሰት

📢 አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክት ከገንዘብ ሚኒስቴር! ⚠️

የገንዘብ ሚኒስቴርን ስምና መለያ (Logo) በመጠቀም ለተለያዩ ክልሎች እና የከተማ አስተዳደሮች "ስለ ስራ ግብር ቅናሽ" ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያዎችና በተለያዩ መንገዶች የሚሰራጨው መረጃ ሙሉ በሙሉ ሀሰተኛ እና ከእውነት የራቀ መሆኑን ሚኒ...

እንቆቅልሽ

ምርጫ ቦርድ የዕጩ ይስሃቅ ወልዳይን ራስን ከምርጫ የማግለል ውሳኔ ውድቅ አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነትን (የኢሕአፓ አባል) ወክለው በአዲስ አበባ ከተማ በአራዳ ክፍለ ከተማ የምርጫ ክልል 1/9 ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዕጩነት የቀረቡት አቶ ይስሃቅ ወልዳይ ራሳቸውን ከእጩነት...

የሀገር ውስጥ ዜና

የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ለታዳጊ አገራት አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠየቁ

የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ፣ ዓለም አቀፍ አጋሮችና የፋይናንስ ተቋማት ለታዳጊ አገራት የነዳጅና ማዳበሪያ መግዣ እንዲሁም ለአነስተኛ አርሶ አደሮች መደጎሚያ የሚሆን አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረቡ። ሚ...

ዜና ትንታኔ

የጽምዶ እና የመከላከያ ውጥረት እስከም ድረስ ይሆን?

የቀንድ አፍሪካ ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ ምህዳር ሁልጊዜም ቢሆን ተለዋዋጭ እና ያልተገመቱ ክስተቶች የሚስተናገዱበት መድረክ ነው። ከሰሞኑ ደግሞ በአዲስ አበባ የሚገኘው የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ ትኩረት የሳበ አንድ አዲስ ወታደራዊ ዲፕሎማሲያዊ...

ንግድ

ኬንያ ከኢትዮጵያ የምታስገባውን የኤሌክትሪክ ኃይል በእጥፍ ልታሳድግ መኾኑ ተገለጠ

ኬንያ ከኢትዮጵያ የምታስገባውን የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን አሁን ካለበት 200 ሜጋ ዋት ወደ 400 ሜጋ ዋት በማሳደግ በእጥፍ ለመጨመር መወሰኗን የአገሪቱ የኢነርጂ ዘርፍ የዜና ምንጮች በስፋት ዘገቡ። ይህ ይፋ የተደረገው የሃይል መጠን ...

የፖለቲካ ፓርቲዎች

ጎጎት ፓርቲ የገዢው ፓርቲ "ስልታዊ" የምርጫ ሕግ ጥሠቶች" ካልታረሙ ራሱን ከምርጫው እንደሚያገል አስጠነቀቀ

ተቃዋሚው የጎጎት ፓርቲ (ጎጎት ለጉራጌ አንድነትና ፍትሕ ፓርቲ) የገዢው ፓርቲ አመራሮች በሁለቱ የጉራጌ ዞኖች ውስጥ መጠነ ሰፊ እና "ስልታዊ" የሆኑ የምርጫ ሕግ ጥሠቶችን እየፈጸሙ ይገኛሉ ሲል በጽኑ ከሰሰ። ፓርቲው ባወጣው ይፋዊ መግ...

የሀገር ውስጥ ዜና

ፌደራል ፖሊስ በእነ ጀነራል አስናቀው ሲሳይ ላይ ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጠየቀ

የፌደራል ፖሊስ ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል የመናድ እንቅስቃሴ በማድረግ በጠረጠራቸው 12 ግለሰቦች ላይ ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ መጠየቁ ታወቀ። ተጠርጣሪዎቹ ከፍተኛ የወታደራዊ መኮንኖችን እና የሃይማኖት አባቶችን ያካተቱ ሲሆ...

የሀገር ውስጥ ዜና

የፖሊሲ ነፃነት ሚስጥር፤ ኢትዮጵያ ቁልፍ መረጃዎቿን በራሷ እጅ ማድረጓ ምን ትርጉም አለው?

በኢትዮጵያ የመረጃ አያያዝ፣ የዲጂታል መሠረተ ልማት እና የፖሊሲ ነፃነት ዙሪያ አዳዲስ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ይፋ መደረጋቸውን ተከትሎ፣ ዘርፉ ወደ አዲስ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑን አመላካቾች እየታዩ ነው። የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢን...

ማህበራዊ - ሚዲያ

የከይር ታይምስ ዘገባዎችን በሁሉም ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች ይከታተሉ